የክራንስተን ጥያቄ ኣላማ ምንድነዉ፥

የ ክራንስተን ጥያቄ የተቋቋመበት ኣላማ በ 24 ህዳር 2021 በለሊት የተከሰተዉን በቻናል ላይ በትንሽ ጀልባ በትንሹ 27 ሰዎች ሂወታቸዉን ያጡበት ክስተት ለማየት ነዉ።

ገለልተኛ ከመንግስት

ይሄ ገለልተኛ ነዉ፡ እናም ህጋዊ ስልጣን የሌለው ጥያቄ ሆኖ መደበኛዉ ኮሮነር ምርመራ በሌለበት የኣማሟታቸዉን ሁኔታ በተመለከተ ሙሉ ምርመራ ለማድረግ እንድያስችል የተነደፈ ነዉ። ይሄ ደሞ ራሱን ችሎ በ ሰር ሮስ ክራንስተን የሚመራ ነዉ።

ገለልተኛ ማለት ደሞ ምርመራው የመንግሥት አካል አይደለም፡ እና ደሞ በመንግስት ክፍል የሚመራ ኣይደለም።

ከእኛ ጋር ይገናኙ

እርሶ ከዛን በ 24 ህዳር 2021 ያጋጠመዉን ክስተት የተረፉ ወይ ደሞ የተጎጂዎችን ቤተሰብ ነህ፥ እንደዛ ከሆኑ፡ ከእርስዎ መስማት እንፈልጋለን። እኛን ማግኘት ከፈለጉ የኛ የአድራሻ ቅጽ (Link to contact form page) በመጠቀም ሊያገኙን ይችላሉ፡ ወይ ደሞ ቀጥለዉ ባሉት ኣማራጮችን በመጠቀም ሊሆን ይችላል፡

ኢሜይል: info@cranston.independent-inquiry.uk

ሜይል: ነጻ ፖስታ የ ክራንስተን ጥያቄ (FREEPOST The Cranston Inquiry)

እርሶን ለማግኘት በኢንግሊዝኛ ነዉ መሆን ያለበት፥

እኛን ለማናገር ከእንግሊዝኛ ዉጪ በሌላ ቋንቋ እንዲሆንሎት ከፈለጉ፡ እባክዎ እኛን ያሳዉቁን እና የኣስተርጓሚ ኣገልግሎት በማቅረብ እርስዎን ማነጋገር እንችላለን።

በጥያቄው ሂደት ውስጥ መሳተፍ እፈልጋለሁ

እርስዎን ወክሎ የሚሰራ ጠበቃ ካሎት፡ እንዴት ሙሉ ተሳታፊ መሆን እንደሚቻል ጠበቃውን ያነጋግሩ ወይ ደሞ በዚ ኢሜይል በመላክ ጥያቄዎን ያቅርቡ info@cranston.independent-inquiry.uk.

ተጨማሪ መረጃ የት ማግኘት እችላለሁ፥

የበለጠ ለማወቅ ድህረ ገጻችንን መጎብኘት ይችላሉ። ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ የችሎት ቀናትን መቼ እንደሆነ ያገኛሉ ፡ በድረ ገጻችን ላይ መረጃ  እና የ ጥያቄዉን ዜና  ።

ጠቃሚ ድርጅቶች

እንደ አለመታደል ሆኖ፣ ስለ ኢሚግሬሽን የሚመለከት ጉዳዮች ላይ መርዳት ወይም ምክር መስጠት አንችልም ይህ ደሞ ከምርመራው ወሰን ውጭ ስለሆነ ነዉ። በኢሚግሬሽን ሁኔታዎ ላይ እገዛ ከፈለጉ ወይም ስለ ጤናዎ የሚያሳስብዎት ከሆነ፡ እባክዎን ከታች ካሉት ድርጅቶች ውስጥ አንዱን ለማነጋገር አያመነቱ፡

Red Cross  

ለ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ፈጣን የጤና እርዳታ ሊሰጥ ይችላል

Migrant Help – ኣሳይለም ሄልፕ ላይን 0808 8010 503

ለ ስደተኞች የምክር ኣገልግሎት እና እርዳታ ይሰጣል

Samaritans -. ወይም ስልክ ቁጥር. 116 123 ነጻ ነዉ

ለሚያስፈልጋቸዉ ሰዎች የመስማት ኣገልግሎት


የክራንስቶን የምርመራ ጥያቄ፡  የማጣቀሻ ውሎች

ወሰን እና ዓላማ

  1. የምርመራ ጥያቄው እ.ኤ.አ. ኖቨምበር 24 ቀን 2021 (ህዳር 15 2014) ቢያንስ 27 ሰዎች በትንሽ ጀልባ ቻናሉን (ባህር) ለማቋረጥ ሲሞክሩ የሞቱበትን ክስተት ይመረምራል፣ ያጣራል ከዛም ሪፖርት ያደርጋል።
  1. ሊቀመንበሩ በነዚህ ክስተቶች ላይ ምርመራ የሚያካሂደው፡-

ሀ. ሟቾቹ እነማን እንደነበሩ፣  መቼ᎓ የት እና በምን ሁኔታ እንደሞቱ ለማረጋገጥ፣

 ለ. እ.ኤ.አ. ኖቨምበር 24 ቀን 2021 (ህዳር 15 2014) ከተፈጠሩት ክስተቶች ምን ተጨማሪ

    ትምህርት ማግኘት እንደሚቻል ለመገምገም እና አስፈላጊ ከሆነም ተመሳሳይ ክስተት  

    እንዳያጋጥም አደጋ ለመቀነስ ሐሳብ ወይም ምክር ለመስጠት ነው።

  1. የምርመራ ጥያቄው ሂደት እና አሰራር በሊቀመንበሩ ይመራል።
  1. ይህንን የምርመራ ጥያቄ ሲያካሂድ ሊቀመንበሩ በባህር አደጋ ምርመራ ቅርንጫፍ (MAIB) ስለ ክስተቱ አስቀድሞ የተደረገውን ምርመራ ግምት ውስጥ ያስገባል።

መርሐግብር

  1. ሊቀመንበሩ በቀጣይም ሆነ ወደፊት የሚደረጉ የህግ ሂደቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በተቻለ ፍጥነት ለትራንስፓርት ሚኒስቴር ፀሀፊ ሪፖርት ያደርጋል። ሪፖርቱን የማሳተም ሃላፊነት ያለበት የትራንስፖርት ሚኒስቴር ፀሀፊ ነው።